top of page

ሕብረት

  • Redeatu G. Kassa
  • Sep 14, 2019
  • 1 min read

እንደ አባቶች ፈለግ እንደ ሐዋሪያት፣

በፊቱ እንደ ተጉት በአንድ ልብ ጸሎት፣

የመንፈስን ሙላት እንደ ተቀበሉት፣

በግልጽ እንደ ናኙት የወንጌሉን ብስራት፣

በኃይል እንደ ሮጡት ለገባቸው እውነት፣

እንዳለቆማቸው ሰይፍና እስራት፣

እንደ ገሰገሱት በአላማ ጽናት፣

እኛም ስንጋጠም ስንቆም በሕብረት፣ ልዩነት ደብዝዞ ሲፈካ አንድነት፣ ለአምላክ ደስ የሚያሰኝ የሚያውድ መስዋዕት፣

በመንፈስ ተሳስረን ስናቀርብ በውበት፣

ሽታችን ይወጣል ይማርካል ነፍሳት። ከራስ እንደ ’ሚወርድ እንደ አሮን ዘይት፣

ይገለጣል በኛ የክርስቶስ ሕይወት፣ ጨለማን የሚገፍ የብርሃን ፍካት።

እኛ ስንያያዝ የአንድ አባት ልጆች፣ ለዘላለም ንጉስ ሲከፈቱ ልቦች፣ እንደ አሴር በረከት ዘይት ሲጠልቁ እግሮች፣

በኃይል እንቆማለን ሆነን ምስክሮች፣

ፊታችን አይቆሙም የገሃነብ ደጆች።


 
 
 

Comments


Recent Posts
Archive
Search By Tags
Follow Us
  • Facebook Basic Square
  • Twitter Basic Square
  • Google+ Basic Square
spotify-badge-button-listen-wh-BG.png
apple-podcasts-logo.jpg
Google-Podcasts-Badge.jpg
RadioPublicc.png
breaker.png
pocketcasts3.png
Anchor-Podcast-Logo.png

 

5850 N. Elston Avenue 

Chicago, Il 60646

10:00 AM TO 12:00 PM SUNDAY

7:00PM TO 9:00PM FRIDAY

  • Facebook Social Icon
  • Twitter Social Icon
  • Google+ Social Icon
  • YouTube Social  Icon
bottom of page