top of page

​እኔ እግዚአብሔር ፈውሼሃለው እመን ብቻ 

 ኣምነህ በጸሎት የለመንከኝን ሁሉ ትቀበላለህ ። የማቴዎስ ወንጌል 21፡22

ኣባቴ እግዚኣብሄር ሆይ ተባረክ። በነገሮች ሁሉ በላይ ኣመሰግናለሁ። 

ጌታና ኣባቴ ሆይ ይህ   (በሽታ  ወይም ህመም)   ኣለብኝ። በቃልህ እንዲ ብለሃል    (ጥቅስ)   እንደቃልህ ፈውሰኝ። ኣባዬ በቃልህ እንዲህ ብለሃል " ኣምኜ በጸሎት የለመንኩትን ሁሉ ትቀበላለህ በየማቴዎስ ወንጌል 21፡22" ላይ። እኔም በልቤ ኣምኜ ጸለይኩ። ኣንተም አንደቃልህ ስለፈወስከኝ ኣመሰግናለሁ። በኢየሱስ ስም ኣሜን   

መዝሙረ ዳዊት

6፡1​፥2

አቤቱ፥ በቍጣህ አትቅሠፈኝ፥ በመዓትህም አትገሥጸኝ። ድውይ ነኝና አቤቱ፥ ማረኝ፤ አጥንቶቼ ታውከዋልና ፈውሰኝ።

መዝሙረ ዳዊት

107 ፡ 18፥20

ሰውነታቸው መብልን ሁሉ ተጸየፈች፥ ወደ ሞትም ደጆች ቀረቡ።  በተጨነቁ ጊዜም ወደ እግዚአብሔር ጮኹ፥ ከመከራቸውም አዳናቸው። ቃሉን ላከ ፈወሳቸውም፥ ከጥፋታቸውም አዳናቸው።

መዝሙረ ዳዊት 

​147፡3

ልባቸውን የቈሰሉትን ይፈውሳል፥ ሕማማቸውንም ይጠግናል።

ትንቢተ ኢሳይያስ​

​53፡5

እርሱ (ኢየሱስ) ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም

ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።

ትንቢተ ኢሳይያስ​

​57፡18​

መንገዱን አይቻለሁ እፈውሰውማለሁ፥ እመራውማለሁ፥ ለእርሱና ስለ እርሱም ለሚያለቅሱ መጽናናትን እመልሳለሁ።

ትንቢተ ኤርምያስ

​30፡17

 እኔ ጤናህን እመልስልሃለሁ ቍስልህንም እፈውሳለሁ፥ ይላል እግዚአብሔር

bottom of page