top of page
Search

ጸሎት አስተምረን -- መንግስትህ ትምጣ (ክፍል አራት)

  • ‎Redeatu G. Kassa
  • Oct 1, 2017
  • 1 min read

“እርሱም በአንድ ስፍራ ይጸልይ ነበር፥ በጨረሰም ጊዜ ከደቀ መዛሙርቱ አንዱ፦ ጌታ ሆይ፥

ዮሐንስ ደቀ መዛሙርቱን እንዳስተማረ እንጸልይ ዘንድ አስተምረን አለው። አላቸውም፦ ስትጸልዩ

እንዲህ በሉ፦ በሰማያት የምትኖር አባታችን ሆይ... መንግስትህ ትምጣ ...” (ሉቃ. 11፡1-2)

ጌታ ባስተማረን ጸሎት አስቀድመን የእግዚአብሔርን አባትነት በመረዳት በልጅነት

መተማመን በፊቱ እንቀርባለን። በመቀጠልም የእግዚአብሔር ስም በሕወታችን እንዲቀደስ

(በእምነትና በልምምድ የእግዚአብሔር ስም በሕይወታችን ተገቢውን ስፍራ እንዲይዝ)

እንጸልያለን። ሌላው በዚህ ጸሎት ማእቀፍ ውስጥ የምናየው ሃሳብ “መንግስትህ ትምጣ” የሚለውን

ነው።

በመንፈሳዊው አለም ሁለት መንግስታት አሉ። የእግዚአብሔር መንግስት አለ፤ የሰይጣን

መንግስት አለ። ጌታችን በምድር አገልግሎቱ ስለ ሁለቱ መንግስታት አስተምሯል። በሉቃስ 12 ላይ

እንደምናነበው ፈሪሳውያን ጌታን “በብዔል ዜቡል በአጋንንት አለቃ” አጋንንትን ያወጣል በማለት

ከሰሱት። ጌታ ግን አሳባቸውን አውቆ “እርስ በርስዋ የምትለያይ መንግሥት ሁላ ትጠፋለች ...

ሰይጣንም ሰይጣንን የሚያወጣ ከሆነ፥ እርስ በርሱ ተለያየ፥ እንግዲህ መንግሥቱ እንዴት

ትቆማለች?... እኔ ግን በእግዚአብሔር መንፈስ አጋንንትን የማወጣ ከሆንሁ፥ እንግዲህ

የእግዚአብሔር መንግሥት ወደ እናንተ ደርሳለች።” (ቁ. 25፣ 26፣ 28) በዚህ ስፍራ በግልጽ

እንደምናነበው ሰይጣን የሚሰራበት የጨለማ መንግስት አለ። ደግሞም የእግዚአብሔር ሃሳብ

የሚከናወንበት የእግዚአብሔር መንግስት አለ። የሰይጣን መንግስት ከእግዚአብሔር መንግስት

ተጻራሪ የሆነ የክፋት መንግስት ነው። የእግዚአብሔር መንግስት በምትገዛበት ስፍራ የሰይጣን

መንግስት የመስራት አቅም የለውም። ተሸናፊ ነው። ስለዚህ ነው ጌታችን “እኔ ግን በእግዚአብሔር

መንፈስ አጋንንትን የማወጣ ከሆንሁ፥ እንግዲህ የእግዚአብሔር መንግሥት ወደ እናንተ ደርሳለች”

በማለት ያስተማረን።

ወንጌላችን የእግዚአብሔር መንግስት ወንጌል ነው። ወንጌል ወደ እግዚአብሔር መንግስት

የምንገባበት መንገድ ነው። እኛም ወንጌሉን የተቀበልን የእግዚአብሔር መንግስት ልጆች ነን። የዚህ

መንግስት ራስ እግዚአብሔር ነው። ስርዓቱ ጽድቅ ነው። ይህ መንግስት በመጨረሻ ሁሉን አሸንፎ

የሚገዛ፣ ሌሎች መንግስታትን ሁሉ እንደ ገላባ የሚያደቅ መንግስት ነው። የእግዚአብሔር

መንግስት በሚገዛበት ስፍራ ሁሉ የእዚአብሔር ህልውና አለ። በዚያ ስፍራ የጨለማ መንግስት

ስፍራ ይለቃል። ስለዚህ የእግዚአብሔር ቃል “አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት

ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል” (ማቴ. 6፡33) ይለናል። ስለዚህም ነው

በአባታችን ሆይ ጸሎት የእግዚአብሔር መንግስትን በመፈለግ የምንጸልየው። (ይቀጥላል)


 
 
 

Comments


Recent Posts
Archive
Search By Tags
Follow Us
  • Facebook Basic Square
  • Twitter Basic Square
  • Google+ Basic Square
spotify-badge-button-listen-wh-BG.png
apple-podcasts-logo.jpg
Google-Podcasts-Badge.jpg
RadioPublicc.png
breaker.png
pocketcasts3.png
Anchor-Podcast-Logo.png

 

5850 N. Elston Avenue 

Chicago, Il 60646

10:00 AM TO 12:00 PM SUNDAY

7:00PM TO 9:00PM FRIDAY

  • Facebook Social Icon
  • Twitter Social Icon
  • Google+ Social Icon
  • YouTube Social  Icon
bottom of page