top of page

ሙት አያመሰግን & ተከፍቷል ሰማይ

ሙት አያመሰግን

እፍ ያለብህ እስትንፋስ

ከስጋህ ሳትገሰስ

ህያው ነፍስ

አምልክ ፈጣሪን

ሙትማ አያመሰግን::

ውደድ እያለህ

ሳይሰበሰብ ገመድህ

አፈር ሳይቀምስ ኣፈር

እያሉ ነው ማፍቀር::

ተከፍቷል ሰማይ

ለአዳም ልጆች አርነት

ወልድ ሲሰቃይ

በሰው ልጅ መስዋእት

ተከፍቷል ሰማይ::

(አዎ ጌታችን በመስቀል ሲውል ሰማይ ከፍቶት ነበር:: ፀሃይ ጨለመች:: ደግም እርሱ የሃጢያት መስዋእት ሆኖ ለተቀበሉት ሁሉ በስሙ ላመኑት የሰማይን በር ከፍቷል::)


Recent Posts
Archive
Search By Tags
No tags yet.
Follow Us
  • Facebook Basic Square
  • Twitter Basic Square
  • Google+ Basic Square
bottom of page