ስለ አራቱ መንፈሳዊ ሕጎች ሰምተዋል?
- Chicago Yemesrach
- Sep 15, 2018
- 1 min read
አንድ፦ እግዚአብሔር ስለሚያፈቅረን ለሕወታችን አስደናቂ እቅድ
ሰጥቶናል። “በእርሱ የሚያምን ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንዲኖረው እንጂ እንዳይጠፋ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን እስኪሰጥ ድረስ ዓለሙን እንዲሁ ወዶአልና።” ዮሐንስ 3፡16
ሁለት፦ ሰው ኃጢአተኛ የሆነ ባህርይ ስላለውና በዚህም ምክነያት ከእግዚአብሔር ስለ ተለየ እግዚአብሔር ለእርሱ ያለውን ፍቅርና እቅድ ሊለማመድ አይችልም። “ሁሉ ኃጢአትን ሠርተዋልና የእግዚአብሔርም ክብር ጎድሎአቸዋል።”ሮሜ 3፡23
ሶስት፦ ኢየሱስ ክርስቶስ ለኛ በመሞቱ በእርሱ በኩል ብቻ ሰው ወደ እግዚአብሔር ይደርሳል። “እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም።” ዮሐንስ 14፡6
አራት፦ ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ አዳኛችንና ጌታችን አድርገን በመቀበል እግዚአብሔር አምላክ ለኛ ያለውን ፍቅርና እቅድ ልናውቅና ልንለማመድ እንችላለን።“ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው።” ዮሐንስ 1፡12
ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስን እንደ ግል አዳኞ አድርገው ለመቀበል ከወሰኑ የሚከተለውን የንስሃ ጸሎት ይጸልዩ ዘንድ እናበረታታዎታለን።
“እግዚአብሔር ሆይ ዛሬ የደህንነትን ወንጌል እንድሰማ እድልን ስለሰጠኽኝ አመሰግንሃለው። እኔ ኃጢያተኛ ሰው ነኝ። ዛሬ ከቅድስት ድንግል ማሪያም ተወልዶ ስለኔ ኃጢያት በመስቀል የሞተውን፣ በሶስተኛውም ቀን ከሞት የተነሳውን ልጅህን ኢየሱስ ክርስቶስን የግል አዳኜ አድርጌ እቀበላለሁ። በልጅህ በኢየሱስ ክርስቶስ ደም ከአጢያቴ ሁሉ አንጻኝ፤ ቀድሰኝ፤ ልጅህ አድርገኝ፤ በመንፈስ ቅዱስም ማህተም አትመኝ። ስላደረክልኝ ምሕረት አመሰግንሃለሁ። በኢየሱስ ክርስቶስ ስም። አሜን!”
Recent Posts
See All“ተስፋን ቃል የሰጠዉ የታመነ ነዉና እንዳይነቃነቅ የተስፋችንን ምስክርነት እንጠብቅ። (ዕብ 10፡ 23) ተስፋ ሰው በሕይወቱ እንደሚሆን በእርግጠኝነት የሚጠብቀው ነገር ነው። እያንዳንዱ ሰዉ ተስፋ የሚያደርገዉ...
ባለንበት ጊዜ በተለይም በ COVID 19 ወረርሽኝ የተነሳ በአብዛኛው ቤት ውስጥ ተከተን ባለንበት በዚህ ወቅት፤ የተለያየ ድምጽ፣ አስተሳሰብ፣ ጩኸት፣ አመለካከት እና ፕሮፓጋንዳ የምንሰማበት አጋጣሚ ሰፊ ነው። በተለይም...
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በተለይም በምእራቡ አለምና በሃገራችን በኢትዮጲያ በተወሰነ መልኩ በትምህርት ቤቶች፣ በአንዳንድ ቢሮዎች፣ በቤትና በአፓርትመንት መስኮቶች ላይ በወረቀት የተቀለመ ህብረቀለማትን አዋህዶ የያዘ...
留言